ስለ ሴቶች የተሰጠ ምክር
፩ ክፉ
ትምህርትን እንዳትማርብህ፥ባጠገብህ በምትተኛ ሚስትህን አታስቀናት፡፡
፪ ኀይልህን
እንዳታደክምብህ፥ለሴት ልብህን አትስጣት፡፡
፫ በወጥመድዋ
እንዳትያዝ የሌላ ሚስት አታባብል፡፡
፬ በዘፈኗ
እንዳታስትህ ከዘፋኝ ሴት ጋር አትጫወት፡፡
፭ ፈቃዷ
እንዳያስትህ ድንግልን አትቈንጥጣት፡፡
፮ ርስትህን
እንዳታጣ ለአመንዝራ ልቡናህን አትስጣት፡፡
፯ በከተማዎቹ
ዙርያ አታማትር፤አደባባይዋም አያስትህ፡፡
፰ ከመልከ
መልካም ሴት ዐይንህን መልስ፤ የሌላ ሚስትም ደም ግባትዋ አያስጐምጅህ፤ በሴት ደም ግባት የሳቱ ሰዎች ብዙዎች ናቸውና፤ስለዚህ
ነገር ፍቅሯ እንደ እሳት ይነድዳል፡፡
፱ ከጐልማሳ
ሚስት ጋር አትቀመጥ፤ ልቡናህን ወደ እርሷ እንዳትወስድ፥ሰውነትህንም በሞት እንዳታሰነካክል በመጠጥ ጊዜ ከእርሷ ጋር
አትቀመጥ፡፡
፲ ድንገተኛ
ወዳጅ እንደ እርሱ አይሆንህምና፥የቀድሞ ወዳጅህን አትተወው፡፡ አዲስ ወዳጅ ጉሽ ጠጅ ነው፤ቢከርም ግን ደስ ብሎህ ትጠጣዋለህ፡፡
፲፩ እንደሚጠፋ
አታውቅምና የኃጥአን ብልጽግናቸው አያስቀናህ፡፡
፲፪ የክፉዎች
ሰዎችም ተድላቸው አያስጐምጅህ፤ እስኪሞቱም ድረስ እንደማይከብሩ ዐስብ፡፡
፲፫ በሞት
ከሚቀጡ መኳንንት ፈጽመህ ራቅ፤ ሰውነትህን እንዳታጠፋ የሞት ጥርጥር አያግኝህ፥ነገር ግን በወጥመድ መካከል እንደምትሄድ፥ በገደልም
መካከል እንደምትመላለስ ዕወቅ፡፡
፲፬ የተቻለህን
ያህል ለባልንጀራህ መልካም አድርግለት፤ ከጠቢባንም ጋር ተማከር፡፡
፲፭ ጉዳይህም
ከዐዋቂዎች ጋር ይሁን፤ ነገርህ ሁሉ በእግዚአብሔር ሕግ ይሁንልህ፡፡
፲፮ ድሆች
ሰዎች በምሳሕ ጊዜ ይኑሩ፤ክብርህም እግዚአብሔርን በመፍራት ይሁን፡፡
፲፯ ሥራው
በብልሃተኛው እጅ ይከናወናል፤የአሕዛብንም አለቃ በቃሉ ጥበብ ያመሰግኑታል፡፡
፲፰ ተናጋሪ
ሰው በከተማው አስፈሪ ነው፥ከቃሉም የተነሣ ፈጽሞ ይጠላል፡፡