፪፤ የእናትንም አገዛዝ በልጆቿ ላይ አክብሯልና ።
፫፤ አባቱን የሚያከብር ልጅ ኃጢአቱይሰረይለታል።
፬፤ እናቱንም የሚያከብራት ልጅ ድልብ እንደሚያደልብ ሰው ነው።
፭፤ አባቱን የሚያከብር ልጅ በልጁ ደስ ይለዋል በለመነበትም ቀን ጸሎቱን ፈጣሪው ይሰማዋል።
፮፤ አባቱን የሚያከብር ልጅ ዘመኑ ይበዛለታል።
፯፤ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ልጅ እናቱን ያሳርፋታል።
፰፤ ባሮቹ ለሱ እንዲገዙለት እሱም ለወለደው ላባቱ ይገዛል።
፱፤ ምርቃቱ ትደርስልህ ዘንድ ቢጠራህ አቤት ቢልክህ ወዴት ብለህ አባትህን አክብረው።
፲፤ ያባት ምርቃት የልጅን ቤት ያጸናልና የናት እርግማን ስር መሠረት ይነቅሳል።
፲፩፤ ልጅባ ባቱ ክብር የሚከብር ስለ ሆነ እናቱንም መናቅ ማቃለል ሰውን የሚያዋርደው ስለሆነ አባትህን መናቅ ማቃለል መመክያ አይሆንህምና አባትህን በመናቅ አትመካ።
፲፪፤ ልጄ በርጅናው ጊዜ አባትህን ኧርዳው በጉልበትም ሳለ አታሳዝነው።
፲፫፤ ቢያረጅ አእምሮውንም ቢያጣ ፈቃዱን ለመፈጸም እሺ በለው ፤ ግን እንደሚቻልህ አክብረው ዋጋ በመቀበል ጊዜ አባትህን መርዳትህ አይዘናጋውምና።ባረጀ ጊዜ አባትህን አትናቀው።
፲፬፤ ስለ ኃጥአትም ፈንታ ጽድቅ ትሰራልሃለች።
፲፭፤ በመከራህም ቀን እግዚአብሔር ያስብልሃል በረድን ጸሐይ እንዲያቀልጠው ኃጢአቶችህ እንደዚሁ ይቀልጣሉ። (ይሰረዩለታል)
፲፮፤ አባቱን የሚጠላ ሰው የተነቀፈ ነው እናቱን የሚያሳዝናት ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነው።
ስለ ትሕትና
ስለ ትሕትና
፲፯፤ ልጄ በሃይማኖትህ ላይ ሥራህ ይገለጥ እውነተኞች ሰዎችም ይወዱሃል።(ድሆች ሰዎች)
፲፰፤ እንደገናንነትህ ብዛት መጠን እንደዚሁ ራስህን አዋርድ። በእግዚአብሔር ዘንድዋጋህን ታገኛለህ ።
፲፱፤ የእግዚአብሔር ሥራው ልውጥ ነውና በተዋረዱ በጸኑ ሰዎች ላይ ይመሰገናል።
፳፤ ከባለጸጋ ጋር አትከራከር የታዘዝከውን አስብ እንጂ የማትችለውን ነገር አትመርምር።
፳፩፤ ወደ እልፍኙ ግን አያገባህም።
፳፪፤ ሥላሴ ከሰው ይልቅ የገለጡህ ምሥጢር የለምና ከግብር ገብተህ ባህርየ ሥላሴን አትመርምር።
፳፫፤ ብዙ ሰዎችን መታለያቸው አሳታቸው ብዙ ሰዎችን የልቡናቸው ትዕቢት በመከራ ጣላቸው።
፳፬፤ ክህደትን የሚወዳት ሰው በሷ ይሞታል ፤ክፉ ልቡናም በፍጻሜ ዘመኑ ለስራ ይያዛል።
፳፭፤ ክፉ ልቡና በመከራ ይገረፋል ኃጢአተኛ ሰውም በኃጢአቶቹ ላይ ኃጢአትን ይጨምራል።
፳፮፤ ክፉ ክህደት ጸንቶባቸዋልና ለትዕቢተኞች ሰዎች ክህደት መመለስ የላትም።
፳፯፤ የብልህ ሰው ልቡና ምሳሌን ይተረጉማል፤ያዋቂ ሰው ዦሮም ጥበብ መስማትን ትወዳለች።
ስለ ምጽዋት
ስለ ምጽዋት
፳፰፤ የምተነድ እሳትን ውኃ ያጠፋታል።እንደዚህም ሁሉ ምጽዋት ኃጢአትን ታስተሰርያለች።
፳፱፤ ምጽዋትን ለሚሰጥ ሰው በፍጻሜ ዘመኑ እግዚአብሔር ዋጋውን ያስብለታል፤ በመከራም በተሰነካከለ ጊዜ የሚድንበት ረድኤት ይገኛል።