፩፤ ልጄ ድኃውን ምጽዋቱን አትከልክለው፤ከሚለምንህ ከድኃውም ዓይኖችህን አትመልስ።
፪፤ የተራበች ሰውነትን አታሳዝን ያዘነ ሰውንም አታበሳጭ።
፫፤ ያዘነ ልቡናንም አታስደንግጥ የሚለምንህን ሰው አልፈኸው አትሂድ።
፬፤ የሚገዛልህ ቤተሰብህን አትቆጣ ከድኃም ፤ፊትህን አትመልስ።
፭፤ ከሚለምንህ ሰው ፊትህን አትመልስ በልቡናው አዝኖ ቢረግምህ ፈጣሪው ልመናውን ይሰማዋልና።
፮፤ ለሚረግምህ ሰው ገንዘብ ምክንያት አትስጠው።
፯፤ በብዙ ሰዎች ዘንድ እንደምትወደድ ሁን ፤ዳኞችን አገልግል ራስህንም አታኲራ።
፰፤ ድኃውን በጆሮህ አድምጠው በየዋህነት በጎ ቃልንም መልስለት።
፱፤ የተበደለውንም ሰው ከሚበድለው ሰው እጅ አድነው ለሱም መፍረድ ቸል አትበል።
፲፤ እናት አባቱ ለሞተበትም ልጅ እንዳባቱ ሁነው ለናቱም እንደ ባሏ ቁምላት እንደ እግዚአብሔር ልጆች እንደ ጻድቃን ትሆናለህ ከናትህ ይልቅ ይወድሃል።
ጥበብ ከፍ ከፍ እንደምታደርግ
ጥበብ ከፍ ከፍ እንደምታደርግ
፲፩፤ ጥበብስ ልጆቿን አገነነቻቸው የሚፈልጓትንም ሰዎች ትቀበላቸዋለች።
፲፪፤ እሷን የወደደ ሰው ሕይወቱን ወደደ ወደሷም የሚገሠግሥ ሰው ተድላ ደስታን ይጸግባል።
፲፫፤ የሚያጸናበትም ሰው ክብርን ይወርሳል እሷም ካደረችበት ዘንድ እግዚአብሔር ያከብራል።
፲፭፤ እሷን የሚሰማት ሰው አህዛብን ይገዛል እሷንም የሚያደምጣት ሰው ከመከራው ተዘልሎ ይኖራል።
፲፯፤ ጠላቱን ፈጽማ እያስፈራራችለት እያስደነገጠችለት ለመከራ እየገረፈችለት ሰውነቱን እስክታስገዛለት ድረስ እያስተማረችው በምክርም እየፈተችው ከሱ ጋራ ጸንታ ትኖር ዘንድ አስቀድማ ትሰጠዋለች።
፲፱፤ ከሷ ወጥቶ ቢስት ግን ትለየዋለች። በሚጥለው በጠላቱም እጅ ትጥለዋለች።
፳፤ ክፉ እንደሆነ አውቀህ ጊዜውን ጊዜውን ተጠበቅ ሰውን አፍሮ ኃጢአት የሚሠራ አለና ሰውነትህን ለመጉዳት ሰው አፍረህ ።
፳፩፤ ፍርድ አታድላ እግዚአብሔርን አፍሮ ጽድቅ የሚሠራ ሰው አለና መወደድን ያገኛል።
፳፪፤ ነገሩ ለሰውነትህ እየተረዳህ የሰው ፊት አይተህ ፍርድ አታድላ ሰውነትህን እንዳታጠፋ ዘንድ አትፈር።
፳፫፤ ከቃሉ የተነሳ ጥበቡ ይታወቃልና ትምህርቱም ባንደበቱ ከመናገር የተነሣ ይታወቃልና የሚናገርን ሰው ቆይ እኔ ልናገር ብለህ አትከልክለው።
፳፬፤ ያልሆነ ሃይማኖት ይዘህ ስለ ሃይማኖት አትከራከር።ስለ በደልኸውም በደል ንሰሐ ገብተህ ተለማመጥ።
፳፭፤ ኃጢአትህንም መነገር አትፈር እንደ ዓባይ ያለውን ውኃ በሃምሌ በነሐሴ እሻገራለሁ አትበል።
፳፮፤ ለሰነፍ ሰው ራስህን አታዋርድ፤ለባለጸጋ አታድላ።
፳፯፤ ፈጣሪህ እግዚአብሔር ስላንተ ይከራከርልሃልና እስክትሞት ድረስ በሃይማኖት አትከራከር።
፳፰፤ ባፍህ አውታታ አትሁን ሥራህንም ቸል አትበል።
፳፱፤ በቤትህም እንደ አንበሳ አትገረም በውነት የሚገዛልህ ቤተ ሰብህንም አታሳዝን።
፴፤ በምትከፍልበት ግዜ ቀኝ እጅህን ትሰበስብ ዘንድ ወደ መሰብሰብ እንዳትመለስ እጅህን አትዘር