Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፶




የኦንያ ልጅ ስምዖን 

፩ የኦንያ ልጅ ታላቁ ካህን ስምዖንም በሕይወቱ ቤተ መቅደስን እደሰ በዘመኑም ቤተ መቅደስን አጸና::

፪ እንዲሁም የቅጥሩን መሰረትም እጥፍ አድርጎ ሠራ ካህን የሚለብደሰን ነጭ ልብስ ሰራ 

፫ በዘመኑም የውሀዋች ምንጮች አልጎደሉም የጉድጓዱም ውኋ ብዛቱ እንደ ባሕር ውኋ ነበር

፬ ሕዝቡም እንዳይወድቁ ይጠነቀቅላቸው ነበር ከተማዋንም ከጠላት ለመከላከል መሸገ :: 

፭ ከቤተ መቅደስ መጋረጃ በወጣ ጊዜም በሕዝቡ መካከል ተከበረ 

፮ በደመና ውስጥ እንደ አጥቢያ ኮከብና በምለዕት ቀን እንደ ሙሉ ጨረቃ ነበር 

፯ በልዑል መቅደስም ላይ እንደምታበራ ፀሀይ ነበረ በብሩህ ደመናም ውስጥ ብርሃንእንደሚስጥ ቀስተ ደመና ነበር 

፰ እንደ መጻው ወራት ጽጌረዳም ነበር በውኋ መፍሰሻ አጠገብ እንደሚያፈራ አበባም ነበር በመከርም ወራት እንደ ሊባኖስ ዛፍ ቅርንጫፍ ነበር

፱ በጥና እሳት ላይ እንዳለ ነጭ ዕጣንም ነበር ተመትቶ እንደርተሰራ የወርቅ እቃም ነበር በጌትጥ ላይ እንዳለ የከበረ እንቁም ነበር

፲ ፍሬዋ ብዙእንደሆነ የዘይት እንጨት ከደመና በታች እንደሚያድግ የዋንዛ ዛፍ ነበር

፲፩ እርሱም የክብር ልብሱን በለብስ ጊዜ የመመኪያውንም ጌጥ በለበሰ ጊዜ ወደ ተቀደሰው መሰዊያ በወጣ ጊዜበቅድስና ልብሱ ተከበረ

፲፪ ከካህናቱም እጅ ከመሥዋዕቱም ሥጋ ክፍል በተቀበለ ጊዜ በመሠዊያው አጠገብ ይቆም ነበር ወንድሞቹም በዙርያው ቆመው ይጋርዱት ነበር እንደ ሊባኖስ ለጋ ዝግባና እንደ ዘንባባም ዛፍ ይከቡት ነበር 

፲፫ እንዲሁም የአሮን ልጆች ሁሉ የክብር ልብሳቸውን ለብሰው የእግዚአብሔርን መባእ በእጃቸው ይዘው በእስራኤል ማህበር ሁሉ ፊት ይቆሙ ነበር

፲፬ በመሠዊያውም ሥራቸውን ይፈጽሙ ነበር ሁሉን የሚችል የሉዑልንም መሥዋዕት ያዘጋጁ ነበር

፲፭ የወይኑን ጽዋ ይዞ እጁን አነሣ የወይኑን ዘለላ ደምም አፈሰሰ ለንጉስ ነገስት ለሉዑል በጎ መዓዛ አድርጎ በመሠዊያው እግር ሥር ያፈስሰው ነበር

፲፮ የአሮን ልጆችም እየጮሁ ምስጋናውን ይናገሩ ነበር ተመትቶ የተሠራ የብር መለከትም ይነፉ ነበር በልዑልም ፊት ማሳሰቢያሊሆንቃላቸውን ያሰሙ ነበር

፲፯ ያን ጊዜም ሕዝቡ ሁሉ በአንድነት ያርፉ ነበር ሁሉንበምድር ላይ በግንባራቸው ይሰግዱ ነበር ሁሉን ለሚገዛ ለሉዑል እግዚአብሔርም ምስጋና ያቀርቡ ነበር 

፲፰ መዘምራኑም በቃላቸው ያመሰግኑ ነበር የዜማቸው ድምጽ ቤቱን ያስተጋባው ነበረ

፲፱ ህዝቡም ወደ ሉዑል እግዚአብሔር ይጸልዩ ነበር በእግዚአብሔር ሕግ ጸንተው ስራቱን እስኪጨርሱ ድረስ ይቅር በሚል በእግዚአብሔር ፊት ይለምኑ ነበር

፳ ከዚህም በኋላ እርሱ ወራዶ እግዚአብሔርን በረከት በአንደበቱ ይሰጣቸው ዘንድ በስሙም ይመኩ ዘንድ በእስራኤል ልጆች ማህበር ልይ እጁን አነሣ 

፳፩ የሉዑልንም በረከት ይቀበሉ ዘንድ ዳግመኛ ሰገዱ

፳፪ አሁንም በሁሉም ቦታ ብዙ ታአምራትን የሚያደርገውን ከእናታችን ማህጸን ጅምሮ ዘመናችንንም የሚያረዝመውን እንደቸርነቱ ይቅርታ የሚያደርግልንን የሁሉን ፈጣሪ አመስግኑ

፳፫ የልቡና ደስታንም ይሰጠናል በዘመናችንም ሰላምን ያደርጋል ለእስራኤልም ለዘለአለም

 
፳፬ በቸርነቱም ከእኛ ጋር የታመነ ነው በዘመናችንም አዳነን 

፳፭ ሰውንውቴ ሁለት ወገኖችን ጠላች ሦስተኛው ግን ሕዝብ አይደለም

፳፮ እነዚህም በሰማርያና በፍልስጤም ተራራ የሚኖሩ በስቂማ የሚኖሩ የአሞሬዋንም ሰዎች ናቸው ጥበብን ከልብ ያነቃል 
የኢየሩሳሌም ሰው የሲራህ አላዛር ልጅ እኔ ኢያሱ ተጥበብና የምክርን ትምህርት በዚህ መጽሐፍ ፃፍኩ

፳፰ ይህን እንደዚህ የሚያደርግ ከዚያም የሚራቀቅ ብጹዕ ነው ይህንን በልቡ የሚጠብቅ ጠቢብ ይሆናል

፳፱ ይህን ይሚይደርግ ሁሉን ይችላል የእግዚአብሔርም ብርሃን ይመራዋል