Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፵፱




ንጉሡ እዮስያስ 
፩ የእዮስያስ መታስቢያ በቀማሚት ብልሃት እንደተቀመመ ሽቶ ነው እንደ ማርም በአፍ ሁሉ ጣፋጭ ነው በመጠጥም ግብዣ ጊዜ እንደ ዘፈን ነው ::   
፪ እርሱ የቀና ነው ሕዝቡንም መለሳቸው የኃጢአትንም ርኩሰት ሁሉ አስወገደ :: 
፫ ልቡናውንም ወደ እግዚያብሔር አቀና በኃጣንም ዘመን ጽድቅን አጻናት:: 
፬ ከዳዊት ከሕዝቅያስና ከኢዮስያስ በቀር ሁሉም በድለዋል
፭ የልዑልን ሕግ ትተዋልና ክብራቸውንም ለሌላ ሕዝብ ስጥተዋልና 
ነቢዩ ኤርምያስ
፮ የተመረጠችውና የተቀደሰችውን ከተማ አቃጠሏት:: መከራ አጽንተውባታልና እንደ ነቢዩ ኤርምያስ ትንቢት ጎዳናዋን አጠፉ::
፯ አሠቅይተውታልና እርሱ ግን ነቢይ ይሆን ዘንድ ይነቅል ዘንድ ያጥፍም ዘንድ እንዲሁም ይተክል ዘንድ ይሠራም ዘንድ በእናቱ ማህጸን ተመረጠ 
ነቢዩ ሕዝቅኤል 
፰ ሕዝቅኤልንም የጌትነኑ ራእይ አየ እግዚያብሔርንም በኪሩቤል ሠረገላ ላይ አየው
፱ ጠላቶቹንም በመዓት አሰባቸው የጻድቃንንም ጎዳናቸውን በመልካም አቀና :: 
፲ የአስራ ሁለቱ ነቢያትም አጽሞቻቸው በቦታቸው ለመለሙ ያዕቆብን አጽናንተውታልና በታመነ ተስፋ አድነውታልና ::
፲፩ ዘሩባቤልን እናገንነው ይሆን እርሱስ በቀኝ እንዳለ እንደ ሐቲም ቀለበት ነው ::
፲፪ የዮሴዴቅ ልጅ ዮሴፅም እንዲሁ ነበር ለዘመናቸውም ቤተ መቅደስ ሰሩ ለዘላለም ክብር ለተዘጋጀ የእግዚያብሔርንም ሕዝብ አከበሩ
፲፫ የነህምያም መታሰቢያ ብዙ ነው የወደቀች ቅጽር አነሳልን ደጃፎችንም አቆመልን ቁልፉንም ሠራልን ቤታችንንም ገነባልን ::
፲፬ እንደ ሔኖክ ያለ ሰው በምድር የተገጠረ የለም እርሱ ከዚህ አለም ተወሰደ 
፲፭ እንደ ዮሴፍ ያለ ሰው አልተወለደም ለወንድሞቹ አለቃ ሆነ ለህዝቡም ኅይል ሆነ ለአጽሞቹም ይቅርይታ አገኝ
፲፮ ሴምና ሴት ከሰው ይልቅ ከበሩ አዳምም ከፈጠረው ሕያው ፍጥረት ሁሉ ከበረ