Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፳፰




፩፤ ለእግዚአብሔር ብሎ መከራውን ለሚታገስ ሰው ጠላቱን ተበቅሎ ያጠፋታል ኃጢያቱንም ያስተሰርይለታል፡፡

፪፤ ባልንጀራህን የምትነቅፈው ኃጢያቱን ይቅር በለው የዚያን ጊዜ ከተለማመጥህ ኃጢያት ህን ያሰሰርይልሃል፡፡ 
፫፤ አንተ ሰው ሆነህ እንዳንተ ያለውን ሰው ሳትቀየም እግዚያብሔርን እንዴት ይቅር በለኝ ትለዋለህ፡፡ 
፬፤ እንዳንተ ያለ ሰው ይቅር ሳትል ኃጢአት ህን ያስተሰርይልህ ዘንድ እንግዲህ እንዴት ትለምነዋለህ ፡፡ 
፭፤ ኃጢአት ህን አስበህ ጠብን ተዋት፡፡
፮፤ ሞትን አስበው ፡ መቃብርንም አስበው ትእዛዙንም ጠብቅ፡፡
፯፤ ሕጉን አስበህ ባልንጀራህን አትቀየም ፡ የእግዚአብሔርን ፍርዱን አስበህ ቁጣውንም አርቃት
፰፤ ቁጣን ክርክርን ተዋት ኃጢአቶች ህንታስነሳቸዋለች ቁጡ ሰው ክርክርን ያነሳሳዋል፡፡ 
፱፤ ሐጢያተኛ ሰው ባልንጀራውን ያደክማል በወዳጆቹም መካከል ነገር ሰርቶ ያጣላል
፲፤ በእንጨቱ ልክ የእሳቱ ነዲዱ ይበዛል በክርክሩም ብዛት ልክ ጠቡን ያበዛል የሰውም ኃይሉ በቁመቱ ልክ ነው በባለጸግነቱ ብዛት ልክ ቁጣውን ያበዛል፡፡ 
፲፩፤ መታበይን የሚያበዛት ሰው ኃጢአትን ይሰራታል ለጠብ የሚቸኩል ሰው ፈጥኖ ደምን ያፈሳል፡፡

                          ክፉ ምላስ

፲፪፤ ፍምን እፍ ብትላት ትነዳለች ትፍም ብትልባት ትጥፋለች ሁለቱም ሁለቱም ሁሉ ከ አንድ አፍ ይወጣሉ፡፡ 
፲፫፤ ብዙ ወዳጆችን አጣልቷልና ፡ አሚተኛ ለ አንዱ አነትን ለ አንዱ አሰትን የሚናገርን ሰው ይረግሙታል፡፡ 
፲፬፤ ነገረ ሰሪ አንደበት ብዙ ሰዎችን አወካቸው ከ አንዱ ወገንም ወደ አንዱ ወገን እንዲሰደዱ አደረጋቸው ብዙ አምባዎችንም አፈረሰች የመኳንንቱንም ቤት አፈረሰች፡፡ 
፲፭፡ ቀባጣሪ አንደበት ሴቶችን ከባሎቻቸው ቤት አስወጥታ ሰደደቻቸው ገንዘባቸውንም አጠፋችባቸው ፡፡ 
፲፮፤ ነገረ ሰሪ አንደበት ያልተጠበቀ ሰው ግን ለዘለዓለሙ ከመከራው አያርፍም በፍቅርም አይኖርም ፡፡
፲፯፤ የግርፋት ቁስል መግል ይይዛል የነገረ ሰሪ አንደበት ቁስል ግን አጥንትን ይሰብራል፡፡
፲፰፤ በጦር ተደብድበው የወደቁ ሰዎች ብዙ ናቸው ነገር ግን በነገሪ ሰሪ አንደበት እንደጠፉ አይደለም፡፡
፲፱፤ ከሷ የዳነ በጥፋቷም ያልተሰነካከለ በስራቷም ያልጸና በግር ብረቷም ያልታሰረ የተደነቀ ነው፡፡ 
፳፤ ሥራቷንም የጸና ሥራት ነው የምታመጣው መከራ ጽኑ ነው፡፡ 
፳፩፤ ሞቷም ጽኑ ሞት ነው ከሷ ሲኦል ትቀላለች፡፡
፳፪፤ በደጋጎች ሰዎች አትደርስባቸውም በእሳት መቃጠልም አያገኛቸውም 
፳፫፤ እግዚአብሔርን የዘነጉ ሰዎች በሷ ይጠፋሉ በማይጠፋ እሳቷም ታቃጥላቸዋለች፡፡ እንደ አንበሳም ትወረወርባቸዋለች እንደ ነብርም ትይዛቸዋለች፡፡
፳፬፤ ገንዘብህን በእሶህ ብታጥር ብርና ወርቕንም ብትቆልፍ፡፡ 
፳፭ ነገርን መጥነህ ብትናገር በ አንደበት ህም አርምሞን ብታኖር ባማረ በተገባ ነበር፡፡ 
፳፮፤ ዳግመኛም በ አንደበት ህ እንዳት ሰናከል በሚያድንህ ጠላት ህም ፊት እንዳትጥልህ ተጠበቅ፡፡