Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፳፯




፩፤ በግብዝነት ሐጢያትን የሚሰሩዋት ብዙ ሰዎች ናቸው ገንዘቡ ይበዛ ዘንድ የሚወድ ሰው ፊቱን ወደ ፍቅረ ንዋይ ይመልሳል፡፡

፪፤ በቅጥር መካከል ድንኳን ይተከላሉ በንግና በዋጋ መካከል ኃጢያት ትመጣለች፡፡

፫፤ እግዚአብሔርን ፈርቶ ካልተጠበቀ የቤቱ ጥፋት አይዘገይም፡፡

              የሕይወት መመዘኛ

፬፤ በወንጠፍት መካከል አሰር ይከማቻል እንደዚሁም ሁሉ ሰውን ኃጢያት ታገኘዋለች፡፡

፭፤ የሸክላ ዕቃን እሳት ይፈትነዋል ሰውንም የልቡናው አሳብ ይፈትነዋል ፡፡ 

፮፤ ተክል የሚጠብቅ ሰው ፍሬውን ያያል እንደዚሁም የሰው ነገሩ የልቡናውን ፍቃድ ይገልጥበታል፡፡ 

፯፤ ሰውን ከስራው የተነሳ ይፈትኑታልና ሰውን ሳትጠይቅ አታድንቀው፡፡ 

፰፤ጽድቅን ብትተክላት ታገኛታለህ እንደከበረ መሉጣ ግምጃም ትለብሳታለህ፡፡

፱፤ ወፍ ከዘመዱ ጋራ ይኖራል ጽድቅም በሚሰሯት ሰዎች ዘንድ ትኖራለች

፲፤ አንበሳ የሚበላውን ያድናል ኃጢያትም የሚሰሩዋትን ሰዎች ታድናለች፡፡ 

፲፩፤ እውነተኛ ሰው ሁል ጊዜ ጥበብን ያስተምራል የሰነፍ ሰው ግን እውቀቱ እየነጋ እንደጨረቃ ይከፈልበታል

፲፪፤ በሰነፎች ዘንድ ጊዜውን ተጠበቅ በብልሆች ሰዎች ዘንድ ግን ሁልጊዜ ነገሩን ተረዳ፡፡

፲፫፤ የሰነፎች ነገር ያበሳጫል ሳቃቸውም የኃጢያት ተድላ ደስታ ነው፡፡

፲፬፤ ብዙ መሐላን የሚምል ሰው ራስ ስቅጥጥ ስቅጥጥ ያደርጋል፡፡ የትዕቢተኛ ሰው ክርክርም ዦሮ ያደነቁራል፡፡ 

፲፭፤ የትዕቢተኞች ክርክራቸው ደም ያስፈሻል ክርክራቸውም ለሚሰማቸው ሰው ድካም ነው፡፡ 

፲፮ ፤ የባልንጀራውን ሚስጢር ያወጣ ሰው መታመኑን አጠፋ ከዚህም በኋላ ወዳጅ አያገኝም፡፡ 
 
፲፯፤ ወዳጅህን ጠብቅ ከእርሱም ጋር ተማመን ሚስጢሩን ብታወጣበት ግን እንግዲህ ፈጽመህ በኋላው አትከተለውም፡፡

፲፰፤ ሰው ጠላቱን እንዳጠፋ የወዳጅህን ወንድሜ ፡ ወንድሜ ማለትን አጠፋህ ፡፡

፲፱፤ ወፍ ከእጅህ እንድታመልጥ ወዳጅህ እንደዚሁ ከአንተ አመለጠህ ፡፡

፳፤ ሚዳቋ ከወጥመድ እንድታመልጥ ፈጽሞ አምልጦሃልና ከዚህ በኋላ አትከተለውም

፳፩፤ ቁስል ቢሆን ተኩሰው ባዳኑት ነበር የተሳደበም ሰው ባካካሱት ነበር የባልንጀራውን ሚስጢር ያወጣውን ሰው ግን ተስፋ ይቆርጡለታል፡፡

                   ስለ ግብዝነት

፳፪፤ክፋቱን ማስተው የሚችል የለምና ባይኑ የሚጠቅስ ሰው ልቡናው ያማረ አይሆንም ፡፡ 

፳፫፤ ለዓይንህ ግን ከንፈሩን ይመጥልሃል በተናገርኸው ሁሉ ያመሰግንሃል ኋላ ግን በቃሉ ይወነጅልሃል በተናገርኸው ቃል ያስጣል፡፡

፳፬፤ የጠላኻቸው ሰዎች ብዙ ናቸው ነገር ግን እንደሱ አይደሉም ፡እግዚአብሔርም እሱን ጠላ፡፡ 

፳፭፤ በባልንጀራው ድንጋይ የሚወረውር ሰው በራሱ ላይ ትወርዳለች፡ የበደል ግርፋት ግን ቁስል ይታወቃል፡፡

፳፮፤ በባልንጀራው ጉድጓድ የቆፈረ ሰው እሱ በውስጡ ይወድቃል ወጥመድም ያዘጋጀ ሰው በወጥመዱ ይያዛል፡፡

፳፯፤ኃጢያት የምትመጣበትን አያውቅም፡፡

፳፰፤ የትዕቢተኞች ስድባቸው ፡ ሳቃቸው እንደ አንበሳ ታድናቸዋለች ተበቅላ ታጠፋቸዋለች፡፡ 

፳፱፤ በደግ ሰው ጥፋት ደስ የሚላቸው ሰዎች በፍዳ ይያዛሉ የሚሞቱበት ጊዜ ሳይደርስ መቅሰፍት ያጠፋቸዋል፡፡

፴፤ ቁጣና መዓትም የሚያስጸይፉ ናቸው ሐጢያተኛ ሰውም ዘንድ ጸንተው ይኖራሉ፡፡