፩ በእነዚህ
በሦስቱ ነገሮች ያማርሁ ሆንሁ በእግዚአብሔርና በሰው ፊትም ያማርሁ ሆኜ ቆምሁ፥ እነዚህም በአንድ ልብ የሚተባበሩ ወንድማማቾች፥ የባልንጀሮች ፍቅር፥ የባልና ሚስትም ስምምነት ናቸው፡፡
፪ ሦስት
ዐይነት ሰዎች ሰውነቴ ፈጽማ ጠላቻቸው፤-ኑሯቸውም እጅግ አበሳጨኝ፤ እነዚህም ትዕቢተኛ ድሃ፥ ንፉግ ባለጸጋና አእምሮ የሌለው
ሴሰኛ ሽማግሌ ናቸው፡፡
፫ ከሕፃንነትህ
ጀምረህ ያልተመከርህ፥ በእርጅናህ ጊዜ እንዴት ብልህ ትሆናለህ?
፬ ሺበት ፍርድ
ሊሰጥ ይገባዋል፤ ሽማግሎችም መምከር ይገባቸዋል፡፡
፭ ለሽማግሎችም
ጥበብ ይገባቸዋል፤ለታላላቅ ሰዎችም ጥበብን መማር ይገባቸዋል፡፡
፮ የትምህርት
ብዛት የሽማግሎች ዘውዳቸው ነው፤መመኪያቸውም እግዚአብሔርን መፍራት ነው፡፡
፯ በልቤ
ያደነቅኋቸው ዘጠኝ ናቸው፤ዐሥረኛውን ግን በቃሌ እናገራለሁ፤እነርሱም በልጆቹ ደስ የሚለው ሰው፥በሕይወቱም ሳለ የጠላቱን ውድቀት
የሚያይ ሰው ናቸው፡፡
፰ ልባም ሴትን
ያገባ ብፁዕ ነው፤በአንደበቱም ያልሳተ ሰው ብፁዕ ነው፤ከእርሱ ላነሰ ሰው ያላደረ ብፁዕ ነው፤
፱ ዕውቀትና
ጥበብን ያገኛት ሰው፥የሚታዘዝላትንም ያገኘ ሰው ብፁዕ ነው፡፡
፲ ጥበብን ያገኘ
ሰው እንዴት ታላቅ ነው!ነገር ግን እግዚአብሔርን መፍራት ይህን ይበልጠዋል፡፡
፲፩
እግዚአብሔርን መፍራት ከሁሉ ትበልጣለች፡፡
፲፪ እርሷንም
የጠበቀ ሰውን የሚመስለው የለም፡፡
፲፫ ከቊስል
ሁሉ ይልቅ የልብ ቊስል ይከፋል፤ ከክፋትም ሁሉ የሴት ክፋት ትከፋለች፡፡
፲፬ በሁሉም
ብትወድቅ በጠላትህ እጅ አትውደቅ፤ ሁሉ ቢበቀልህ ጠላትህ አይበቀልህ፡፡
፲፭ ከእባብ
ራስ የሚከፋ ራስ የለም፤ ከጠላትም ቂም የሚከፋ ቂም የለም፡፡
የክፉ ሴት ተግባር
፲፮ ከክፉ ሴት
ጋራ ከምትኖር፥ ከአንበሶችና ከምድር አውሬዎች ጋር መኖር ይሻላል፡፡
፲፯ ክፋትዋ
መልኳን ይለውጠዋል፤ ፊትዋንም እንደ ድብ መልክ ያጠቊረዋል፡፡
፲፰ ባሏንም
በባልንጀሮቹ መካከል ይንቁታል፤ መራራ ኀዘንንም ያሳዝኑታል፤ አስጨንቀውም ይይዙታል፡፡
፲፱ ክፋት ሁሉ
ከሴት ክፋት ታንሳለች፤ እርስዋም ወደ ኀጢአት ዕድል ታደርሳለች፡፡
፳ የአሸዋ
ዐቀበት የሽማግሌዎችን እግራቸውን እንደሚያደክም፥ እንዲሁ ቀባጣሪ ሴት የዋህ ባልን ታደክመዋለች፡፡
፳፩ የሴት
መልኳ አያስትህ፤ሀብቷም አያስጐምጅህ፡፡ መቅሰፍትና ጥፋት ጽኑ ውርደትም ናትና፤
፳፪ ሴት ባሏን
ብትመግበው፥ ቊጣን፥ አለማክበርንና ብዙ ዘለፋን የተሞላች ትሆናለች፡፡
፳፫ ለልብ
ቊስል ናት፥ ለፊትም ጥቁረት ናት፥ ለነፍስም ኀዘን ናት፤ እንዲሁ ባሏን የማታከብር ሴት እንደ ሽባ እጅና ልምሾ እንደ ሆነ እግር
ናት፡፡
፳፬
በመጀመርያም ኀጢአት ከሴት ተገኘች፤ በእርስዋም ምክንያት ሁላችን እንሞታለን፡፡
፳፭ ለውኃ
መፍሰሻ አታብጅለት ለሴትም የልብህን ምሥጢር አታውጣላት፡፡
፳፮ እንደ
ጠባይህ ካልሆነች ፍታት፤ ከሰውነትህም ለያት፡፡