Saturday, October 5, 2013

ምዕራፍ ፳፮



                              የደግ ሴት ተግባር

፩፤ ደግ ሴትን ባሏ ያደንቃታል በህይወት የሚኖርበትም ዘመን እጥፍ ይሆናል ፡፡ 

፪፤ የበሬ ወገን የሆነች ሴት ባሏን ደስ ታሰኘዋለች ዘመኑንም በደስታ በተድላ ይጨርሳል፡፡

፫፤ የደግ ሴት እድሏ ያማረ ነው እግዚያብሔርንም የሚፈራ ሰውንም ወደ እድሉ ታደርሰዋለች ፡፡

፬፤ የባለጸጋውም የድሃውም ልቡ ያማረ ይሁን ሁል ጊዜም ፊቱ የበራ ይሁን፡፡ 

                               ስለ ክፉ ሴት
 
፭፡ በእነዚህ በሶስቱ ነገሮች ልቦናየ ደነገጠብኝ አራተኛውም ልቦናየን፡ አስፈራኝ ፡ይኸውም ያገር ወንጀል የ አህዛብ መሰብሰብ ሰውን ለሞት የሚያደርስ አሰተኛ ምስክር ነው፡፡ 

፮ ባሏን ከውሽማዋ ጋራ የምታቀና ሴት የልብ ቁስል ናት የሰውነትም ኀዘን ናት ፡በመከራው ሁሉ የነገረ ሠሪ አንደበት ከመጣው ግርፋት ጋራ ትተካከላለች፡፡ 

፯ደረቅ ሴት ውልቅ ውልቅ እንደሚል እንደበሬ ቀንበር ናት ከእሷም ጋራ የሚኖር ሰው ጊንጥ እንደሚጨብጥ ሰው ነው፡፡

፰፤ አፍረቷን የማትሸፍን ሰካር ሴት ጽኑ ጥፋት ናት ፡፡

፱፤ የሴት ዝሙቷ በ አይኗ ይታወቃል ፡ በቅንድቧም ይታወቃል፡፡

፲፤ ስታ እራሷን እንዳታጠፋ ልጅህን አጥንተህ ጠብቃት፡፡

፲፩፤ የሚጎዳህ ነገር ቢኖር ትጽጸት ዘንድ ወደመጸጸት እንዳትመለስ ከባሏም ፈቃድ እንዳትወጣ አድርግ

፲፪፤ የተጠማ ሰው ጭቃውን እንዲልስ ከቀረበውም ውኃ እንዲጠጣ በእንጨት ስርም እንዲያርፍ ፡፡

፲፫፤ አርበኛ ፍላፃውን፡ ከጉራንጉሬው ፈጥኖ እንዲያወጣ ሰሰኛ ሴትም ከቤቷ መዘዝ ብላ ፈጥና ትወጣለች፡፡

                           የደግ ሴት በረከት

፲፬፤ የሴት መወደዷ ባሏን ደስ ያሰኛል፡፡

፲፭፤ ጥበቧም ሰውነቱን ያድሰዋል

፲፮፤ የዋህ ሴት ለእግዚያብሔር እድሉ ናት

፲፰፤ ሰውና እግዚያብሔርን የምታፍር ሴት በበረከት ላይ በረከትን ታገኛለች፡፡

፲፱፤ ነገር ለምትታገስ ሴት ለውጥ የላትም ፡፡

፳፤ ፀሐይ እግዚያብሔር በፈጠረው ሰማይ ሆኖ እንዲያበራ እንዲሁ የደግ ሴት ጌጧ ባማረ በቤቷ ውስጥ ነው፡፡

፳፩፤ የደብተራ ኦሪት ፋና በመቅረዟ ላይ እንድታበራ እንደዚሁ የብልህ ሰውም ግብሩ በመልኩ ይታወቃል፡፡

፳፪፤ በብር ሰክተት ላይ የቆሙ የወርቅ ምሰሶዎች ደስ እንዲያሰኙ በበጎ ስራ ጸንቶ የሚኖር የደግ ሰው እግር አገባብም እንደዚሁ ደስ ያሰኛል፡፡

፳፫፤ በነዚህ በሦስቱ ነገሮች ልቦናየ አዘነብኝ ፡፡

፳፬፤ አራተኛው ግን ብስጭትን አመጣብኝ

፳፭፤ መጀመሪያ አርበኛ ጨካኝ የሆነ ሰው የሚበላው የሚጠጣው አጥቶ ቢቸገር ነው፡፡

፳፮፤ ሁለተኛም አዋቆች የሆኑ ሰዎች ከእግዚያብሔር ህግ ወጥተው ቢስቱ ነው፡፡

፳፯፤ ሦስተኛው ጽድቅን ትቶ ወደ ሐጢያት የሚመለስ ነው፡፡

፳፰፤ እንዲህ ያለውን እግዚያብሔር በጦር ያጠፋዋል፡፡

፳፱፤ አንጥረኛ ከሐጢያት በጭንቅ ይድናል መሸተኛም ከሐጢያት ተመልሶ አይጸድቅም፡፡