፩. በሰው
ተፈጥሮ ያለ ሞትን መጠራጠር ጽኑ ነው ከናታቸው ሆድ ከተወለዱ ጀምሮ በሁሉ እናት በመቃብር ሆድ እስኪቀረበሩ ድረስ በአዳም
ልጆች ላይ የከበደ ሸክም ሞት አለ፡፡
፪. የምታስደነግጥ
ናት ልብንም የምታስፈራ ናት በመንግሥት ዙፉን ካለ ንጉሥ ጀምሮ ባመድና በትቢጣ ላይ፡፡
፫. እስከሚተኛ
ድሀ ድረስ ዕለተ ሞትን መጠራጠር በአዳም ልጆች ላይ ሁሉ አለ፡፡
፬. ቁጣ ቅናት
ገዝንዝ ሰው ማወክ ሞትን መፍራት፡፡
፭.ክርክር
ሰውን ማማት ይህ ሁሉ በሰው ልቡና አለ ነገር ግን በመኝታው በተኛ ጊዜ የሌሊት እንቅልፍ አሳቡን ይለውጠዋል፡፡
፮. ዕረፍቱም
እንደ ኢምንት ጥቂት ነው፡፡ ይህ ሁሉ በመኝታው ይታወቃል አንድ ጊዜ እንደ ሸንጎ ተከማችቶ ያገኘዋል የልቡናውን ምክር
የሚያወላውላት ሰው በሰልፍ እንደሚሸሽ ሰው ይናገራታል፡፡
፰. ይህ ሁሉ
እስከ ከብት ድረስ በሰው ላይ አለ ይህም በኃጢአተኞች ሰዎች ላይ ሰባት እጥፍ ይብሳል፡፡
፰. ሰልፍ
መታበይ ቸንፈር ጦር ቀጠና የልብ ቁስል መቅሠፍት፡፡
፱. ይህ ሁሉ በኃጢአተኞች
ሰዎች ላይ ኜተጠረ ስለነሳቸውም ኃጢአት የጥፋ ውኃ መጣ፡፤፤
፲. ሁሉ
ከምድር ተፈጠረ ሁሉም ወደ ምድር ይመለሳል የወንዙ ውኃ ሁሉ ወደ ውቅያኖስ ይለሳል፡፡
፲፩. ሰዎችም
ሁሉ ወደ መቃብር ይለሳሉ ከህደት ትጠፋለች ሃይማት ግን ለዘለዓለሙ ትፀናለች፡፡
፲፫. ሠርቆ
ቀምቶ ያጠራቀሙት ገንዘብ እንደ ፈሳሽ ውኃ ፈጥኖ ይጠፋል ዝናም በዘመነ ጊዜ መብረቅ ተሰምቶ እንዲጠፋ እንደዚያ ፈጥኖ
ይጠፋል፡፡
፲፬.
እግዚአብሐየር ሥልጣኑን በገለጠ ጊዜ ደስ ያሰኛል የሚክዱት ሰዎች ግን ፈጽመው ይጣሉ፡፡
፲፭.
የኃጢአተኞች ሰዎች ልጆች ልጆቻቸው አይበዙም የኃጢአተኞች ሰዎች አባትነታቸው በሚያድጥ አለት ላይ እንደ ወደቀዘር ነው፡፡
፲፮. ዝናም
በሁሉ ላይ ይዘንማል በወንዝ ዳር ያለ አኻያ ከፈላ ከቀጤማ ተለይቶ ተነቃቅሎ እንዲወድቅ አባትነታቸው እንዲዚያ ይጠፋል፡፡
፲፯. ይግዚአብሔር
ስጦታ ግን በበረከት ጊዜ እግዚአብሔር እንደ ፈጠራት እንደ ገነት ነው፡ ምጽዋትም ለዘላለሙ ጸንቶ ይኖራል፡፡
፲፰. በገንዘብ
የተዘጋጀው ሰው ሕይወቱ የሀበላው የጠጣው ቢስማማው ነው፡ ከነዚህም ከሁለቱ ይልቅ ተቀበረ ወርቅ ማግኘት ደስ ያሰኛል፡፡
፲፱. ያገር
ሕንፃና ልጆችም ስምን ያስጠራሉ፡ ከነዚህም ከሁለቱ ይልቅ የተቀበረ ወርቅ ማግኘት ደስ ያሰኛል
፳. ዘፈንና
ወይን ልቡናን ደስ ያሰኛሉ ከነ ዚህም ከሁለቱ ይልቅ ጥበብን መውደድ ደስ ያሰኛል፡፡
፳፩ በገናና
መሰንቆ ሰውነትን ደስ ያሰኛታል ከሁለቱም ይልቅ ልዝብ አንደበት ደስ ያደኛል፡፡
፳፪ ደም ግት
ከመልክ ጋራ ዓይንን ደስ ያሰኛታል፡፤ ከሁለቱም ይልቅ ቡቃያ ደስ ያሰኛል፡፤
፳፫ አማችና
ወዳጅ በዘመናቸው ይጠቀውማሉ ከሁለቱ ይልቅ ደግ ሴት በሏን ስት ታሰኘዋለች፡፡
፳፬. ረዳትና
ወንድሞችም በመከራ ቀን ይጠቅማሉ፡ ከሁለቱም ይልቅ ለማዳን ምጽዋት ትሻላለች፡፡ ፤
፳፭. ብርና
ወርቅ አገር ያጸናሉ ከሁለቱ ይልቅ በጎ ምክር ደስ ታሰኛለች፡፡
፳፮. ገንዘብና
ባለጸግነት ልቡናን ደስ ያሰኛሉ ከሁለቱ ይልቅ እግዚአብሔርን መፍራት ይበልጣል
፳፯. እግዚአብሔርነ
መፍራት የምታሳጣው የለም አጋዥም አትሻ፡፡ እግዚአብሐየርን መፍራ በረከቷ እግዚአብሀየር እንደ ፈጠራት እንደ ገነት ናት ተድላ
ደስታና ክብርም በሷ አለ፡፡
፳፰. ልጄ
በጉልበት ሳለህ ልመናን አትውደዳት ከመለመን ሞት ይሻላል፡፡
፳፱. የሌላ
ማዕድ ደጅ የሚጠና ተስፋ የሚያደርግ ሰው አነዋወሩ እንደ ሞተ ሰው ነው እንጂ እንደ ደህነኛ አይደለም የሰው እህል የሚወድ ሰው
ከሐሜት አይድንም የተመከረ አዋቂ ሰው ግን ከሁሉ ይጠበቃል፡፡
፴. ለማያፍር ሰው አፍ ልመና ያማረ ነው
በሆዱ ግን አሳት ትነዳለች፡፡