Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፴፫




፩. የፍፁም ኃይል ፈጣሪ አቤቱ ቅር ብለህ ከመዓት ወደ ምሕረት ተመለስልን፡፡ 

፪. በአሕዛበ ሁሉ አንተን መፍራት አሳድር፡፡

፫. ልዩ በሆኑ ወገኞችንም ሥልጣንህን ግለጥ ኃይልህንም ይዩ፡፤ 

፬. እነሳቸው የኛን ጥፋት ሲያዩ በኛ ጥፋት እንደተመሰገንህ እንደዚሁም ሁሉ እኛ የነሳቸውን ጥፋት ስናይ በነሳቸው ጥፋት ተመስን፡፡ 

፭. አቤቱ ያላንተ ሌላ ፈጣሪ የለምና እኛ እንዳወቅንህ እነሱም ይወቁህ፡፡ 

፮. ታምራትህን አሳይ ጌትነትህንም ግለጥ፡፡ 

፯. በሥልጣንህ ኃይል በከበረ ሥልጣንህም

፰. ጥፋትን አምጣባቸው መቅሠፍትንም አምጣ፡፡ 

፱. በደለኖችን አጥፋቸው አንጥያኮስንም አጥፋቸው፡፡ 

፲. የባሮችህን መሐላ አስብ የሚጠፉበትነም ቀን ፈጥነህ አድርጋት፡፡ 

፲፩. በእሳት አጠፋቸው ከነሳቸው ያመለጡትንም በጦር አጥፋቸው በወገኖችህም ክፉ ያደረጉ ሰዎችን ሞት ያግኛቸው፡፡ 

፲፪. ያለኛ ሌላ ሰው የለም የሚሉ የጠላቶችን አለቆችን ሥልጣን አጥፋ፡፡ 

የያዕቆብን ልጆች ሁሉ ሰብስባቸው፡፡