ስለ ህልም ከንቱነት
፩.ሰነፍ ሰው ግን
አሰተኛ ህልምን በከንቱ ተስፋ ያደርጋታል አሰተኛ ህልምም ሰነፍ ሰውን ያስደነግጠዋል
፪. አሰተኛ ህልምን
የሚያምን ሰው ጥላን እነደሚጨብጥ ነፋስንም እንደሚከተል ሰው ነው
፫ ህልም ካለመሆን
ወደ አለመሆን ይሔዳል በየምሳሌውም እየራሱ ያሳይሃል
፬. ካህያ ምንም
ምን መስዋት የሚሆን በግ አይወለድም ከሃሰተኛ ህልምስ እውነተኛ ነገር በየት ይገኛል፡፡
፭. ሐሰተኛ ህልም
ጥንቆላ ሟርት ሁሉም ከንቱ ናቸው ልቡናንም ያስደነግጣሉ እንደምጥም ያጎብጣሉ፡፡
፮. ሐሰተኛ ህልም
ብዙ ሰዎችን አስቷቸዋልና እሱንም ተስፋ እያደረጉ ጠፍተዋልና፡፡
፯. ይቅር ይል
ዘንድ ከእግዚአብሔር የተገኘ ካልሆነ አሰተኛ ሕልምን በልብህ አታኑረው፡፡
፰. ያለ ሐሰትስ
ከታየ በውነት ይደርሳል እውነተኛ ሕልምም የተረዳ ይሆናል፡፡
፱. የተማረ በመከራ የተገሰጸ ሰው ብዙ ምስጢር ያውቃል መከራን የተቀበለ ሰውም
ጥበብን ያስተምራል፡፡
፲. በትምህርት
ያልተነካ ሰው ግን የሚያውቀው ነገር የለም፡፡
፲፪. መከራ በተቀበልኩ
ጊዜ ብዙ ምስጢር አየሁ አስቤ ከተውኩትም የተናገርሁት ነገር በዛ፡፡
፲፫. ለሞት እስክደርስ
ጊዜ ድረስ ሁልጊዜ መከራ ተቀብያለሁና ስለዚህ ነገር፡፡
፲፬. እግዚአብሔር ከመከራ ያድነኛል፡፡ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሰውነት ከመከራው
ትድናለች፡፡
፲፭. እሱን ያመኑ
ሁሉ ይድናሉ
፲፮. እግዚአብሔርን
የሚፈራ ሰውን የሚያስፈራው የለም እሱ አለኝታው ነውና መከራ መጥቶበት አይደነግጥም፡፡
፲፯. እሱ ያድርበታልና የታመነ ወዳጁም ነውና፡፡
፲፰. እግዚአብሔርን
የምትፈራ ሰውነት የተደነቀች ናት፡፡
፲፱. ኃይልነቱ
የታመነ ነውና ረድኤቱም ጽኑ ነውና የእግዚአብሔር አይኖቹ የሚፈሩትን ሰዎች ይመለከታሉ በረሃውን ያቀዘቅዝልሃል ከቀትር ጸሃይም ይሰውርሃል
ከመከራ ይጠብቅሃል ረድቶም ከመከራ ያድንሃል፡፡
፳. ሰውነትህን
ያገናታል አይኖችህንም ያበራቸዋል ከደዌ ይፈውሳል ደኅንነትንም ይሰጣል በረከትንም ይሰጣል፡፡
፳፩. የበደል መስዋት
ተጠላ ነው ኃጢያተኞችም ቁርባናቸው አደፈኛ ነው፡፡
፳፪. ሕግ የዘነጉ
ሰዎች መስዋዕትን አይቀበልም፡
፳፫. በመባህ ብዛት
ኃጢአትህን የሚያስተሰርልይህ አይደለም፡፡
፳፬. ልጁን ባባቱ
ፊት የሚገድለው ሰው ደስ እንዳያሰኝ ሰርቆ ቀምቶ መባ የሚያገባ ሰው እንደዚያ ደስ አያሰኝም፡፡
፳፭. የድሃ ህይወቱ
ምጽዋት መለመን ነው፡፡ እምቢ ያለው ሰው ግን ነፍሰ ገዳይ ነው፡፡
፳፮. ባልንጀራውን
ገደለ ሰው ደስ እንዳያሰኝ፤ ነገር ሰርቶ ባልና ሚስትንም የሚያፋታ ሰው የባልንጀራውን እንደገደለ ሰው ነው፡፡
፳፯. የምንደኛውን
ደመወዝ የቀማ ሰው ደሙን ማፍሰሱ ነው፡፡
፳፰. አንዱ ሲሰራ
አንዱ ቢያፈርስ የሁለቱስ ድካማቸው ምን ይጠቅማል፡፡
፳፱. አንዱ ቢመርቅ
አንዱ ቢረግም ከሁለቱ የማናቸውን ቃል ይሰማል፡፡
፴. ሬሳ ከዳሰሰ
በኋላ እጁን ቢታጠብ ዳግመኛ ሬሳውን ከዳሰሰ የፊተኛው መታጠብ ምን ይጠቅመዋል፡፡
፴፩. ስለ ኃጢአቱ የሚጾም ሰው ዳግመኛ ይበድል ዘንድ ቢሄድ ከዚህ በኋላ ጸሎቱን
ማን ይሰማዋል ሰውነቱንስ ማሳዘን ምን ይጠቅመዋል ፡፡