Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፴፬




፩. የሚጣፍጥ እህልን በጎ ልቡናህን አይንቁትም ለበለጸግነት መትጋት ፈጽሞ ሰውነት ያከሳል ገንዘብህንም ማሰብ እንቅልፍ ያሳጣል፡፡ 

፪. የሚጠራጠሩት ጠላት መኖርም በንጉልቻ እንቅልፍ ያስረሳል ጽኑ ቁርጥማት ያተጋል እንቅልፍም ያሳጣል፡፡ 

፫. ባለጸጋ ገንዘብ ያደልብ ዘንድ ይዞራል ያረፈም ጊዜ በጥጋብ ደስ ይለዋል፡፡ 

፬. ድሀ ገንዘብ በማጣት ይደክማል ባረፈም ጊዜ ወደ ልመና ይመለሳል፡፡

፭.ገንዘብ የሚወድ ሰው አይጸድቅም ኃጢአትንም የሚዋት ሰው ይከተላታል፡፡ 

፮.ገንዘብ ወደው የጠፉ ሰዎች ብዙ ናቸው ሞታቸውንም በፊታቸው አዩአት፡፡ 

፯. ገንዘብ ለሚፈልጓት ሰዎች እንቅፋት ናት ሰነፍ ሰው ሁሉ በሷ ይሰነካከላል፡፡

፰. ከኋጢአት ንጹሕ የሆነ ባለጸጋ ልቡናውንም ወደ ገንዘብ ያልወሰደ ባለጸጋ የተደነቀ ነው፡፡ ለወገኖቹ በጎ ነገር ያደረገ ማነው እንጃ እናድንቀው፡፡ 

፲.በገንዘቡ ያወቀበት ከሕግም ወጥቶ ያልሳተ ሰው ማነው እንጃ እናድንቀው እሱም መመኪያ ሆነው ኃጢአት መሥራት ሲቻው ኃጢአት የማይሠራ ማነው፡፡ 

፲፩.ክፉ መሥራት ሲቻለው ክፉ የማያደርግ ሰው ማነው እንጃ እናድንቀው በረከቱ ትጸናለች ምጽዋቱም በአሕዘብ አግር ትሰማ፡ 

  የማዕድ ሥርዐት

፲፪.በታላቅ ማዕድም ብትቀመጥ ለመብላት ጉሮሮህን አትክፈት፡ (ሁሉን ውጬው አትበል) በውሰጡም ብዙ ሥሩ አትበል 

፲፫.ሰው ኣይን ክፉ እንደ ሆነ አስብ ከሰው ዓይን የሚከፋ ምን አለ ስለዚህም ነገር የሰውን ዓይን ታላቅሳለች፡፡

፲፬.ላየኀው ሁሉ አትሳሳ ዘእጅህን አትንከር ድስቱን ወዳንተ አትትት ድስቱን አንጥረግ፡፡ 

፲፭.ባልንጀራህ ያቀረበልህን ሁሉ እወቅ ያቀረበልህንም ሁሉ ተረዳ፡፡ 

፲፮.ያቀረቡልህን እንደ ብልህ ሰው ሁነህ ብላ ባልንጀራህን እንዳታስጸይፍ ስታላምጥ አፍህን አታጩህ፡፡

፲፯.ከሰው ሁሉ አስቀድመህ ተው አትሳሳ እንደማይጠግብ ሰው አትሁን፡፡ 

፲፰.በሰው መካከልም ብትቀመጥ እጅህን አስቀድመህ አታውርድ፡፡ 

፲፱.በመኝታህ ሆድህን እንዳይከብድህ ጥቂት እንደሚበቃው እንደ አዋቂ ሰው መጥነህ ብላ፡፡ 

፳. ሰውነቱን የሚመጥናት ሰው እንቅልፍ ጤና ነው ከእንቅል በጧት በተቀሰቀሰ ለጊዜ ሆዱን አይከብደውም ለማይጠግብ ለስሱ ሰው በሽታው ቁንጣን ጓታና ብሰና ነው፡፡ 

፳፩. ትበላ ዘንድ ግደ ቢሉህ ቀድመሃቸው ተነስ ከመብላትም እረፍ፡፡ 

፳፪. ልጄ አድምጠኝ ምክሬንም አትናቅ ኋላ ነገሬን ታገኘዋለህ ምንም እንዳታጣ በሠረኸው ሥራ ሁሉ ደካማ አትሁን፡፡ 

፳፫. ለጋስን ሰው በሥራው ማማር ይመርቁታል ንፉግ ሰውንም በክፉ ሥራው ይረግሙታል፡፡ 

፳፬. መጠጥ ብዙ ሰዎችን አስቷቸዋልና ወይን በጠጣህ ጊዜ አትታበይ፡፡ 

፳፭. ጽኑ ብረትን በወናፍ ይፈትኑታል እንደዚሁም ሁሉ የትቢተኞችን ልቡናቸውን ወይን ይፈትነዋል፡፡ 

፳፮. የሰው ደግንነቱ ወይን መጠጣት ነው መጥኖ ለሚጠጣም ሰው ተድላ ደስታው ነው እሱ ለሰው ተድላ ደስታ ሊሆን ተፈጥሯልና ወይን ለማይጠጣ ሰው  ደህንነቱ ምንድነው፡፡ 

፳፯. ለልና ፈጽሞ ተድላ ደስታ ነው ወይንን መጥኖፐ በጊዜው መጠጣት ደግ ነው፡፡ 

፳፰. ወይን የልቡና ኃዘንን ያስረሳል ለሚያለቅስ ለሚያዝንም ሰው ወይን አጣጣው 

፳፱. ሰነፍ ሰው ወይን በጠጣ ከገዜ ክርክር ያበዛል ደስታል ይበድላል የመጠጥ ብዛት ኃይል ይሰጣል ቁስልም አያሳጣ፡፡ 
 
፴. ወይን ጠጥቶ ሳለ ባልንጀራህን አትቁጣው ልቡናው ደስ ብሎት ሳለ አታሳዝነው የምትነቅፈውንም አትንገረው እሱ ሰክሮ ሳለ ጉዳይህንም አትለምነው፡፡