ነብዩ ኤልያስ
፩ ነቢዩ
ኤልያስም እንደ እሳት ተነሳ ቃሉም እንደ ነበልባል ያቃጥል ነበር::
፪ ረኃብንም
አመጣባቸው በቅንዓቱም አሳነሳቸው ::
፫ በእግዚአብሔርም ቃል ሰማይን ዘጋው ከሰማይም እሳትን ሦስት ጊዜ
አወረደ::
፬ ኤልያስ ሆይ
በታእምራትህ እንዴት ከበርህ እንዳንተስ የተመካ ማንነው?
፭ በልዑል ቃል ከሞቱ ሰዋች ለይቶ ሞትን ከመቃብር ያስነሣ ማንነው?
፮ ነገሥታቱን ወደ ሞት የከበሩ ሰዎቹንም ከአልጋቸው ያወረዳቸው ማንነው?
፯ በሲና
የእግዚአብሔርን ተግሣጽ በኮሬብም የበቀልን ፍርድ የስማ ማንነው?
፰ ይበቀሉ ዘንድ ነገሥታቱን ከእርሱም ቀጥሎ ይተኩ ዘንድ ነቢያትን
የቀባቸው ማንነው?
፱ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ወደ ሰማይ የወጣ ማንነው?
፲ መቅሠፍቱ ከመውረዱ አስቀድሞ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመልስ ዘንድ
የአባትንም ልብ ወደ ልጅ ይመልስ ዘንድ የያዕቆብንም ወገኖች ያጻናቸው ዘንድ በተወሰነ ዘመን የተጻፈለት ማንነው?
፲፩
የሚያውቁህና በፍቅርህ ያጌጡ ሰዎች ብፁዓን ናቸው እኛም ስለ አንተ በህይወት እንኖራለን ::
ነብዩ ኤልሳዕ
፲፪ በእሳት
ሰረገላ ወደ ላይ የወጣ ኤልያስ ነው ከእርሱም መንፈስ የተመላ ኤልሳዕ ነበር በዘመኑም አለቆች አላስደነገጡትም ማንም እርሱን
የተቋቋመው አልነበረም ::
፲፫ ከነገሩም
ሁሉም የተሳነው አልነበረም ከሞተ በኋላ በድኑ ትንቢትን ተናገረ ::
፲፬ በሕይወቱም
ሳለ ድንቅ ተአምራትን አደረገ በሞቱም ሥራው ድንቅ ነበረ ::
፲፭ ከዚህም
ሁሉ ጋር ሕዝቡ ንስሓ አልገቡም ከሀገራቸውም ተማርከው እስኪሄዱ ድረስ ኅጢአታቸውን አልተውም በሀገሩም ሁሉ ተበተኑ ከህዝቡም
ጥቂት ሰዎች ቀረ::
፲፮ ከእነርሱም ደግ ስራ የሰሩ ነበሩ ኅጢአትም ያበዟት ነበሩ
ንጉሡ ሕዝቅያስ
፲፯ ሕዝቅያስም ከተማውን አጸና በመካከልዋም ውኃን አስገባ ዓለቱንም በብረት
ቁፈረ የውኃ መስኖ አሠራ
፲፰ ስናክሬምም
በዘመኑ ዘመተ ራፋስቂስንም ላከው ወደ እርሱም ሄዶ በጽዮን ላይ እጁን አነሣ ታበየ አፉንም ከፍ ከፍ አድርጎ ተናገረ ::
፲፱ ያን ጊዜ
ልቦናቸው ደነገጠባቸው እጃቸውም ዛለ እንደምትወልድ ሴትም ምጥ ያዛቸው ::
፳ ይቅር ባይ እግዚያብሔርንም ለመኑት እጃቸውንም ወደ እርሱ አነሱ ቅዱሱም
ከሰማይ ፈጥኖ ሰማቸው በኢሳይያስም እጅ አዳናቸው ::
፳፩ የአሦርንም ሠራዊት አጠፋ መላኩም አጠፋቸው ::
፳፪ ሕዝቅያስ
እግዚያብሔርን ደስ የሚያሰኝው ሥራ ሠርቷልና በራእዪ ታላቅና ታማኝ የነበረው ነቢዩ ኢሳይያስም እንዳዘዘው የአባቱ የዳዊትን
መንገድ አጽንቷልና ::
፳፫ ፅሐይም
በዘመኑ ከመሄድ ወደ ኋላ ተመልሳለች የንጉሡም ዘመን ጨመረለት :: በታላቅ መንፈስ በመጨረሻ የሚሆነውን አየ በፅዮን
የሚያለቅሱትንም አጽናናቸው ::
፳፬ ለዘላለሙ
የሚሆነውን የተሰወረውንም ሳይሆን ተናገረ ::