፩፤ ባፉ
ያልተስነካከለ ሰው የተደነቀነ ነው። ኃጢአተኛ ሰውን ግን መንፈሳዊ ኃዘን አያስደነገጠውም።
፪፤ ኃጢአት ሠርቶ ሰውነቱን የሚያሳዝን አለኝታውንም የሚያጣ ሰው
የተደነቀነ ነው።
ሀብትን በሚገባ ስለ መጠቀም
፫፤ ነገር
ለማያውቅ ሰው ሹመት አይገባውም፤ ለንፉግም ሰው ገንዘብ አይገባውም።
፬፤ ሰውነቱን
የሚነፍጋት ሰው ለሌላ ሰው ያከማቻል፤ ሌላ ሰው ግን በገንዘቡ ደስ ይለዋል።
፭፤ ሰውነቱን
የሚነፍግ፥ በገንዘቡም ደስ የማይለው ሰው ለማን ይሰጥ ዘንድ አለው።
፮፤ ሰውነቱን ከሚነፍግ ሰው የሚከፋ የለም፤ ለክፋቱም እሱም ፍዳ
ይሆነዋል።
፯፤ በጎ ሥራም
ቢያደርግ ባረጀ ጊዜ ብቻ ነው ኋላም ኃጢአቱ ይገለጣል።
፰፤ የንፉግ ሰው ዓይን ክፉ ነው፤ ከድሀ ፊቱን የሚመልስ ሰውነቱን ቸል
ይላል።
፱፤ ለስሱ ሰው
ዓይን እድሉ አያጠግበውም፤ የልቦናውንም ንፍገት ሰውነቱን ያከሳዋል።
፲፤ የንፉግ
ሰው ዓይኑ እህል ይነፍለጋል፥ በማዕድም ይነፍለጋል።
፲፩፤ ልጄ፦
የሚቻልህን ያህል ሰውነትህን አዘጋጃት፣ በሚገባህ ገንዘብ ለእግዚአብሔር መባ አግባ።
፲፪፤ ሞት
እንዳይቀር አስብ፥ የምትሞትባትም ቀን ትቀራለች ብለህ አትጠራጠር።
፲፬፤
በተድላህ፥ በደስታህ ጊዜ እንዳትታጣ ሁን፤ በጎ እድልም አያምልጥህ።
፲፭፤ ገንዘብህን ለባዕድ ትተዋለህና ወራሾችህ ገንዘብህን ሁሉ ይካፈላሉ።
፲፮፤ ገንዘብህን
አንሥተህ ስጥ፤ በመቃብር የምታገኝው፥ ተድላ ደስታ የለምና ሰውነትህን ደስ አሰኛት።
፲፯፤ ሕግ ቢያፈርሱ ሞት ተፈጥሯልና ሰው ሁሉ እንደ ልብስ ይጠፋል።
፲፰፤ ቅጠሉ ጭፍቅ ያለ፥ የእንጨት ቅጠል፣ የመጀመሪያው ቅጠል እንዲረግፍ
ደማዊና ሥጋዊ ፍጥረት ሁሉ እንዲሁ ነው፤ ይህ ይወልዳል ያ ይሞታል።
ጥበብን በመፈለግ የሚገኝ ደስታ
፳፤ ነገር
ግን፥ ንስሐ ገብቶ የሞተው፣ ሕጉንም የጠበቀ፣ በገንዘቡም ያወቀበት ሰው የተደነቀነ ነው።
፳፪፤ ጥበብን
ተከተላት፥ ምሥጢሯንም መርምር ሥራቷንም ጠብቅ።
፳፫፤ መስኮቷን
የሚጐበኝ ባደባባይዎቿም ተቀምጦ የሚያዳምጥ።
፳፬፤ በቤቷም
አጠገብ የሚኖር፥ በዙሪያዋም የድንኳኑን ካስማ የሚተክል።
፳፭፤ ሰውነቱን
በሥልጣኗ የሚያስጠብቅ፥ ባማረ ማደሪያዋም የሚኖር።
፳፮፤ ልጆቹንም በረድኤቷ የሚያስጠብቅ፥ በዘጠኙም ሕግጋት ጸንቶ የሚኖር።
፳፯፤ በሷም
ከመከራው የሚያርፍ፥ በክብሯም ጸንቶ የሚኖር ሰው የተደነቀነ ነው።