Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፴፭




፩. አለቃም አድርገው ቢሾሙህ ራስህን አታኩራ ከነሳቸው አንዳንዱ ሁሉ አዘናቸውንም እዘን ተቀምጠህም ፍረድላቸው፡፡

፪.ፍርድህን ጨርሰህ እረፍ መልክትህንም ጨርሰህ የክብር ዘውድን ታኝ ዘንድ ከሳቸው ጋራ ደስ ይልህ፡፡ 

፫.ሽማግሌ ይገባሃል ተናገር ለበጎ ነገር ቸል አትል የጥበብህንም ነገር ተናገር፡፡ 

፬.ለመረመረህ ሰው ሁሉ ምሥጢርህን አትናገር አንዳገኘህም አትራቀቅ፡፡ 

፭.በውርቅ ጌጥ ያለ የከበረ ዕንቁ ያማረ የተወደደ እንደ ሆነ ዘፈንም ወይን በሚጠጡ ሰዎች ዘንድ እንደዚሁ ያማረ እንደ ሆነ መሰንቆና ዘፈንም እንደሱ በመጠጥ ቤት ያማረ የተወደደ ነው፡፡

፮. ጉልማሳ ካሰናበቱህ ተናገር በጭንቅ ተናገር ዳግመኛም ቢጠይቁህ፡፡ 

፰.አንድ ጊዜ ተናግረህ ዚያን ጊዜ ነገርህን ጨርስ እያቅህም ባንደበትህ ዝም በል፡፡ 

፱.በመኳንንት መካከል አትቀመጥ ሌላ ሰው ሲናገር ነገርህን አትናገር 

፲. መብረቅ ከነጐድግድ በፊት እንደሚሮጥ እንዲሁ የሚያርፍ ሰው መከበሩ ከፊቱ ነው፡፡
 
፲፩. ወደ ቤትህ ገብህ ሁሉን በጊዜው ጊዜ መጥህ አድርግ በዚያም ደስ ይልህ ተጫወት፡፤ 

፲፪. የሚገባውን የሚወደደውን ሁሉ አድርግ ትእቢትን ነገር እንዳትናገር እወቅ በቃልህም አትበድል፡፡ 

፲፫. ከዚህ ሁሉ ጋራ ፈጣሪህን አመስግነው እሱም ከበረከቱ ሁሉ ያጠግብሃል፡፡ 

         ሕግን መተርጐም

፲፬. እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ለሕጉ ይገዛል ወደሱም ፈጥነው የሚሄዱ ሰዎች ፈቃደቸውን ያገኛሉ፡፡ 

፲፭. ሕጉንም የሚጠብቀው ነው ሕን ከመጠበቁ የተነሣ ይጠግባል የሚጠራጠር ሰው ግን በሱ  ይፈፋል ይስታል፡፤ 

፲፮. ለሚፈሩት ሰዎች መአውግዚአብሔር ይፈርድላቸዋል በፍላ ባለጸግነትም ሳሉ ጠላታቸውን ተበቅ ያጠፋላቸዋል፡፡

፲፯. ኃጢአተኛ ሰው ግን የሚመክሩትን ሰዎች አይስማም መሁሉም እደ ልቡ ይመስለዋል፡፡ 

፲፰. ብልህ ሰው ያለምክር የሚሠራው ሥራ የለም የሚያዝን ጠላት ትቢተኛ ያለምክር ሥራውን ሠርቶ ፍርሃትን ያደርጋል፡፡ 

፲፱.ልጄ አንተ ግን ያምክር የመትሠራው፡፡ ሥራ የለም የሠራኸውንም ሥራ አታጥፋ፡፡ 

፳. በጥፋት ድንጋይ እንዳተሰነካከል ፈጽመኅ በምድረ በዳ አትሑድ፡፡ 

፳፩. ጠላትህን በምድረ በዳ አትመነው፡፡ በፈቃድህ ጸንቶ የሚኖር ልጅህን ስንኳ አትመነው፡፡

፳፪.  በሠራኸው ሥራ ሁሉ ሰውነትህትን ደስ አሰኛት በሁሉም ትዕዛዙን ጠበውቅ፡፡ 

፳፬. ሕን የሚጠብቅ ሰው የነመጻፉን ትዕዝ ይሰማል በአግዚአብሔርም ያመነ ሰው የሚያጣው ነገር የለም፡፡