Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፴፪


፩. ሕጉን የሚጠብቅ ሰው መባ ያገባል፡፡ 

፪. ትዕዛዙን የሚሰማ ሰው ድህነቱ ሊደረግለት መሥዋዕት ይሠዋል፡፡ 

፫. ስንዴ የሚያገባ ሰው ዋጋውን ይመልሳል፡፡ 

፬. ምጽዋት የመጸወተ ሰው የምስጋና መሥዋዕትን ሠዋ፡፤

፭. የእግዚአብሔር ደፈቃዱ ኃጢአት እንዳትሠራ ነው ከበደልም ትርቅ ዘንድ ፈቃዱ ነው፡፡

፮. ወደ እግዚአብሔር ማደሪያ ወደ ቤተ ክርስቲያ ባዲህን አትግባ፡፡

፯. ይህ ሁሉ ስ ትዕዛዙ አድርግ፡፡ 

፰. የደግ ሰው ምሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል መዓዛውም ወደ እብዚአብሔር ይደርሳል፡፡ 

፱. የደግ ሰው መስዋዕት የከበረ ነው ስም አጠራሩም ሁሉ አይዘነጋበትም፡፡ 

፲. ፊትህን ደስ እያለህ እግዚአብሔርን አመስግነተው ከመጀመሪያ አዝመራህም አሥራት መግባተን አትተው፡፡ 

፲፩. የሰጠህን ገንዘብ ሁሉ ፊትህን ደስ እያለህ ስጠው ደስ እያለህም ያዝመራህን አሥራት አግባ፡፡ 

፲፪. እንደ ክብሩ ብዛት መጠት ለእግዚአብሔር መባህን አግባ በጅህ ካገኘኀው ገንዘብም ፊትህን ደስ እያለው አግባለቴ፡፡

፲፫. እግዚአብሔር ዋሃግን ይመልስልሃልና ሰባት እጥፍም አድር ይሰጥሃልና ፊትህን ደስ እያለህ አግባለት

፲፬. አይቀበልልህምና መማለጃን አታግባለት፡፡ 
 
፲፭.እግዚአብሔር የውት ዳኛ ነውና ፊትን አይቶም አያዳላምና የበደልን መስዋዕት የሚቀበል አይምሰልህ፡፡ 

፲፮. ይሐውንም ስለ ችጋሩ ከባለጸጋው አይለየውም የተበደለ ሰውንም ጩኸት ይሰማል፡፡

፲፯. እናት አባት የሞቱበት ልጅ ልመናን ቸል አይልም ባልቴት ሴትንም ያስለቀሳት ሰው ቢኖር

፲፰. እንባንም በፊቷ ላይ ብታወርድ፡፡ 

፲፱. እንዚሁ ባአለቀሰት ሰው ላይ አንባ ይወርዳል፡፡ 

፳. በውነት የሚያገለግለውን ሰው ልመናውን ይቀባዋል ልመናውም ወደ እግዚአብሔር ትደርሳለች፡፡

፳፩. የድሀውም ልመና ወደ አግዚአብሔር ትደርሳለች ወደሱ አስክትደርስ ደርሳ አትመለስም እግዚአብሔርም እስኪያያት ድረስ ደርሳ አትመለስም፡፡ 

፳፫. ለደጋግ ሰዎች ይፈርድላቸዋል ጠላታቸውንም ተበቅሎ ያጠፋላቸዋል የጠላታቸውን ሥልጣን እስኪያጠፋ ድረስ ስለነሳቸው ፈጽሞ ቸል አይልም፡፡ 

፳፬. አሕዛብን ተቀብሎ ያጠፋቸዋል፣ በደለኞችንም ሁሉ ያጠፋቸዋል የኃጢአተኞችንም ሥልጣን ያጠፋታል፡፡ ለሰው ሁሉ እንደ ሥራው ዋጋውን ይፍለዋል የወገኖቹን በቀል ይመልሳልና በቸርነቱም ደስ ያሰኛቸዋልና፡፡

፳፭. ስለ ሰዎችም ሁሉ እንደ ሥራቸው እንደ ሥራቸው ፍዳውን ይከፍላቸዋል፡፡ 

፳፮. ዝናም ያዘ ደመና መበበረሃ ደስ እንዲያሰኝ በመከራው ጊዜ ከይቅርታን የሚያገኘ ሰው የተደነቀ ነው፡፡