Sunday, October 6, 2013

ምዕራፍ ፴



ስለ ልጆች

፩፤የውሉዱን፣ነገር፣የሚናገር፣አንቀጽ፣ይህ፣ነው::ልጁን የሚወድ፣ሰው፣በሱ፣ደስ፣ይለው፣ዘንድ፣ልጁን፣መቅጣትን፣ቸል፣አይልም::

፪፤ልጁን፣ያስተማረ፣ሰው፣በልጁ፣መናገር፣ያመሰግኑታል በወዳጁም፣ዘንድ፣መመኪያ፣ይሆነዋል::

፫፤ ልጁን፣ያስተማረ፣ሰው፣ጠላቱን፣ያስቀናዋል፣በወዳጆቹም ዘንድ፣በልጁ፣መማር፣ደስ፣ይለዋል::

፬፤ከሱ፣በኋላ፣እንደሱ፣ያለ፣ልጅ፣ተክቷልና፣አባቱም፣ቢሞት እንዳልሞተ፣ይሆናል::

፭፤ለጠላቶቹ፣የሚመክት፣ለወዳጆቹ፣የሚፈተፍት፣ከሱ፣በኋላ እንደሱ፣ያለ፣ልጅ፣ተክቷልና::

፮፤በሕይወቱም፣ሳለ፣በልጁ፣ደስ፣ብሎታልና፣ቢሞትም፣ልቡ አያዝንም::

፯፤ከልቅሷቸው፣የተነሣ፣ሰውነትህ፣ይነዋወጣልና፣ልጆችህን ስለማስተማር፣ልቡናህን፣አሳዝን::

፰፤ ያልተገራ፣ፈረስ፣ገርጋሪ፣ይሆናል፣ያልተማረ፣ልጅም አውታታ፣ሆኖ፣ያድጋል::

፱፤ ልጅህን፣ካቀማጠልከው፣ይበረታታብህ፣ዘንድ፣ወደ መበርታት፣ይመለሳል፣ከሱም፣ጋራ፣ብትጫወት፣ያሳዝንህ ዘንድ፣ወደ፣ማሳዘን፣ይመለሳል::

፲፤ እንዳያሳዝንህም፣አትሳቅለት በፍጻሜ፣ዘመንህም ጥርስህን፣ያረግፍሃል::

፲፩ ፤ በጒልማስነቱ፣ሳለ፣ልጅህን፣አትቅጣው::

፲፪፤ ባደገ፣ጊዜ፣እንዳይከዳህ፣በልጅነቱ፣ጐን፣ጐኑን፣ግጠበው::

፲፫፤ በሱ፣ጥፋት፣አንተ፣እንዳታፍር፣ልጅህን፣አስተምረው ያገለግልሃል::

     ስለ ጤንነት

፲፬፤ ሰውነቱ፣ከታመመ፣ሆዱ፣ከታሠረ፣ባለጸጋ፣ሰውነቱ ጤነኛ፣የሆነ፣ሆዱ፣የተከፈተ፣ድሀ፣ይሻላል::

፲፭፤ ሰውነትህ፣ጤነኛ፣ይሁን፣ሆድህም፣የተከፈተ፣ይሁን፣ከገንዘብና፣ከባለጸግነት ሁሉ ይህ ሰውነቱ፣ጤነኛ፣የሆነ፣ድሀ ይሻላል::

፲፮፤ በጤና፣ከመኖር፣ባለጸግነት አይወደድም ከልቡና፣ተድላ ደስታም፣የሚሻል፣ሌላ፣ተድላ፣ደስታም፣የለም::

፲፯፤ ከማያልፍ፣ችጋር፣ከቊርጥማትም፣በሽታ፣ሞት፣ይሻላል::

፲፰፤በተዘጋ፣አፍ ፊት የቀረበ፣መብል ደስ እንዳያሰኝ፣እንደዚሁ ወደ መቃብርም እህልን የሚወስድ ሰው ደስ አያሰኝም::

፲፱፤ እነሳቸው አይበሉ አይጠጡ አያሸቱ ለጣዖቶች መሥዋዕት መሠዋት፣ምን ይጠቅማል እግዚአብሔርም በደዌ የቀሠፈው ሰው እንደዚሁ ነው::

፳፤ጃንደረባ፣ቆንዦይቱን ባቀፋት ጊዜ እንዲያዝን ባይኖቹ እያየ፣ያዝናል::

፳፩፤ ልቡናህን የብስጭት ኅዘን አታሳዝን ሰውነትህንም፣አታበሳጭ::

፳፪፤የልቡና፣ተድላ ደስታ፣ለሰው ሕይወቱ ነው የልቡና ተድላ፣ደስታም፣ዘመንን፣ያበዛል::

፳፫፤ሰውነትህን፣አለዝባት የብስጭት ኅዘን፣ብዙ ሰዎችን አጥፍቷቸዋልና፣የብስጭት ኅዘንን የምትጠቅመውም የለምና የብስጭት ኅዘንን ካንተ፣ታርቅ ዘንድ ልቡናህንም አረጋጋት::

፳፬፤ ቊጣና ቅናት በሕይወት የሚኖርበትን ዘመን፣ያሳንሳሉ የብስጭት፣ኅዘንም ጊዜው ሳይደርስ ያስረጃል::

፳፭፤ አጫጅን እየተከተለ የሚቃርም ሰው ማታ፣በራት እንዲተካከል እኔም፣ከነቢያት በኋላ፣ተነሥቼ በእግዚአብሔር፣ረድኤት ከነቢያት ማዕርግ ደረስኩ::

፳፮፤ ይራቀቁ ዘንድ ለሚወዱ ሰዎችም ሁሉ ነው እንጂ የደከምኩ ለኔ ብቻ፣እንዳይደለ እነሆ፣አስተውሉ::

፳፯፤ በሕዝቡ ላይ የተሾማችሁ መኳንንት ስሙኝ የአሕዛብም አለቆች፣አድምጡኝ::

፳፰፤ ሚስትህና ልጅህን ወዳጅህና፣ወንድምህንም አንተ በሕይወት ሳለህ፣በገንዘብህ አታሠልጥናቸው ኋላ፣እንዳትጸጸት በቤትህም ባዕድ አትሹም ትለምናቸው ዘንድ ወደ መለመን እንዳትመለስ፣በሕይወት ሳለህ፣በገንዘብህ፣ላይ አታሠልጥናቸው::

፳፱፤አንተ፣በሕይወት ሳለህ አእምሮህም ሳለች ግብርህን አትለውጥ::

፴፤አንተ፣የልጆችህን እጅ ደጅ ከምትጠና፣ልጆችህ አንተን ቢለምኑህ፣ይሻልሃል:: 

፴፩፤በሠራኸው፣ሥራ፣አዋቂ፣ሁን፣በሾሙሁም፣ቦታ፣ሁሉ ራስህን፣አታዋርድ::

፴፪፤በሕይወት፣የኖርህበት፣ዘመንህ፣ሁሉ፣ባለቀ፣ጊዜ የምትሞ ትባትም፣ቀን፣በደረሰች፣ጊዜ፣የዚያን፣ጊዜ፣ገንዘብህን፣አውርስ::

፴፫፤ አህያህን፣ገለባ፣አብላው፣ጫነው፣ባለንጋ፣ባኮርባጅ ግረፈው፣ቅጣው፣መግበው፣ግዛው::

፴፬፤ባሮችህን፣ግዛቸው፣ዕረፍት፣ታገኛለህ፣ብታቦዝናቸው፣ግን፣ይከራከሩህ፣ዘንድ፣ካንተም፣ነጻ፣ይወጡ፣ዘንድ፣ይወዳሉ::

፴፭፤ቀንበር፣መጫን፣አንገትን፣ዝቅ፣ያደርገዋል፣ክፉ፣ባሪያንም፣አለንጋ፣እግር፣ብረት፣ያለዝበዋል::

፴፮፤ባሪያህን፣ግዛው፣ቦዘን፣ብዙ፣ክፋትን፣ታስተምራለችና::

፴፯፤አቦዝነህም፣አታኑረው::

፴፰፤የሚችለውን ያህል፣ሥራውን፣ስጠው፣ባይገዛ፣ግን፣እግር ብረቱን፣አጽናበት፣ያለ ምክር፣የምትሠራው፣ሥራ፣አይኑር ነገር፣ግን፣ሥጋዊውን፣ደማዊውን፣ሁሉ፣አትመነው::

፴፱፤ደግ፣ቤተ፣ሰብእ፣ቢኖርህ፣እንደ፣ወንድምህ፣አድርገው እንደ፣ሰውነትህም፣ ውደደው::

፵፤ክፉ፣ነገር፣ብታደረግ፣ግን ይኮበልልብሃል፣ያመልጥሃል ከዚህ፣በኋል በየት ጎዳና፣ታገኘዋለህ::