Saturday, October 5, 2013

ምእራፍ ፳፪



                                 ሰነፍ እና ስንፍና

፩ ሰነፍ ሰው በተቀመጠበት ቦታ እንደ ዋሻ ደንጊያ ነው በጽኑ ስንፍናው ሁሉን ያቦዝናል::

፪ ፫ ሰነፍ ሰው በተኛበት ቦታ እንደሚያጸይፍ ፈረስ ነው:: የገደለው ሰው ሁሉ የጁን ትቢያ ማራገፉ ነው:: ያልተማረ ልጅ ላባቱ እፍረት ነው ሰነፍም ልጅ የጎሰቆለች ትሆናለች::  

፬ ብልህ ሴት ልጅ ባሏን ትወርሰዋለች ሰነፍ ልጅ ግን ላባቷ ኅዘን ናት::

፭ ሁለጊዜ ሰባት እጥፍ ጉስቁልናን ትጎሰቁላለች አባቷንም ታሳፍራለች ባሏንም ታሳፍራለች ደፋርም ናት::  

                                 ጥበብ እና ሞኝነት

፮ ባገኘበት ቦታ ነገሩን የሚናገር ሰው በልቅሶ ቤት መሰንቆ እንደሚመታ ሰው ነው:: ግርፋት ከቁጣ ጋር ሁልጊዜ ብልህ ያደርጋል:: 

፯ ሰነፍ ሰውን የሚያስተምረው ሰው የተሰበረ ገልን እንድ እንደሚያደርግ ሰው ነው የተኛ ሰውን ከጽኑ እንቅልፍ ቀስቅሰው:: 

፰ ለሰነፍ ሰው የሚናግር ሰው ለተኛ ሰው እንደሚነግር ሰው ነው ተናግረኸው ከጨረስክ በሁዋላ ምን ተናገርህ ይልሃል:: 

፱ ተድላ ደስታው አልፏልና ለሞተ ሰው አልቅስለት አእምሮው ጠፍቷልና ለሰነፍ ሰውም አልቅስለት::

፲ ከሞተ በኋላ አይመለስምና ለሞተ ሰው ታለቅስለት ዘንድ አግባብ ነው:: ከመሞቱ መኖሩ ይከፋበታልና ለሰነፍ ሰው ግን በሕይወት እያለ አልቅስለት::  

፲፩ ለሰነፍ ሐጥያተኛ በሕይወት በኖረበት ዘመን አልቅስለት::

፲፪ ከሰነፍ ሰው ጋር ነገር አታብዛ አእምሮ ከሌለውም ሰው ጋር አትኑር ወደ መከራ እንዳያገባህ አንተም በሱ ስንፍና እንዳትነቀፍ ተጠበቅ::

፲፫ ከሱ ራቅ ሰውነትህም ታርፋለች ይቀልሃል በሱ ስንፍናም አንተ የምትጎዳው የለም::  

፲፬ ከአረር የሚከብድ ምን አለ ሰነፍ ከመባልስ በቀር የሚከፋ ምን አለ:: 

፲፭ ከሰነፍ ሰው ጋር ከመኖር ጨውና አሸዋ የብረት ወገን ናስንም ብትሸከም ይሻላል::

፲፮ ማገሩ ያማረ በካብ ላይ ያለ ካቡ በተናደ ጊዜ ማገሩ እንዳይፈታ ያዋቂ ሰው ምክርም በጽኑዕ ልቡና እንደሱ ነው:: 

፲፯ ሁል ጊዜ ጽናቱ ማገር ነው በግድግዳ ላይ ያሸዋ ምርግ እየተቀረፈ እንዲወድቅ:: 

፲፰ በነፋስ ፊት ያለ ገለባም ነፋስ በነፈሰ ጊዜ እንዳይቆም የሰነፍ ሰውም አሳብ የሰደበው ሰው ቢኖር ቆሞ የማይዋጋ በፈሪ ሰው ልቦና ዘንድ እንደሱ ነው::

፲፱ አይኑን የጠነቆሉት ሰው እንባውን ያወርዳል ልቡናውንም በትምህርት ያደሰ ሰው ጥበብን ያሳያል::

፳ በወፎች ደንጊያ የወረወረባቸው ሰው ያባርራቸዋል በወዳጁም የሚለገድ ሰው ወንድሜ ማለትን አጠፋ::

፳፩ በወዳጅህ ሰይፍን ብትመዝ አፍህንም በሱ ከፍና ዝቅ አድርገህ ብትናገር ወዳጅ እንደሚሆንን መጠን ተስፋ አትቆርጥለትም::

፳፪ ብትለገድበት አፍህንም በሱ ክፉና ዝቅ አድርገህ ብትናገር ብትሰድበው ምክሩንም ብታወጣበት ብትከዳው ብታሳዝነውም ነው እንጂ ወዳጅ እንድሚሆንህ መጠን ተሰፋ አትቁረጥለት በዚህ ነገር ወዳጅ ሁሉ ይሸሻል:: 

፳፫  አንተም ድሀ ብትሆንም በተድላው በደስታው ጊዜ ከሱ ጋራ ደስ ይልህ ዘንድ ከባልንጀራህ ጋራ ሃይማኖትህን ጠብቅ ርስቱን ባገኘ ጊዜ ከሱ ጋራ ደስ ይልህ ዘንድ ቢቸገርም ከሱ ጋራ መከራውን ታገሥ::  

፳፬ የእሳት የጪሱ ተንታ ይቀድማል እንደዚሁም ደም ከማፍሰስም ጠብና ክርክር ይቀድማል::

፳፭ ወዳጄን መሰወር አላፍርም ከፊቱም አልሠወርም::

፳፮ ነገር ግን ስለሱ መከራ ብታገኘኝ የሰማ ሁሉ ሰሱ ራሱን ይጠብቅ::

፳፯ ላንደበቴ ጠባቂ ማን ባኖረልኝ በነሳቸው እንዳልጠፋ አንደበቴም  እንዳትገድለኝ ባንደበቴ የጥበብን ቁልፍ ማን ባኖረልኝ::