፩፤ ጥቅም
የሌላቸው ብዙ ልጆችን አትውደድ፥ በክፉ ልጆችም ደስ አይበልህ።
፪፤ በነሳቸው
እግዚአብሔር መፍራት ከሌለባቸው፥ ቢበዙም በነሳቸው ደስ አይበልህ።
፫፤ በሕፃንነትም
ሳሉ አትመናቸው፥ ብዛታቸውም ደስ አያሰኝህ። ከሺህ ልጆች አንድ አዋቂ ልጅ ይሻላል፥ ክፉ ልጅም ከመውለድ ሳይወልዱ መሞት
ይሻላል።
፭፤ ዓይኔ
እንዲህ ያለ ብዙ ነገሮች አየች። ከዚህም የሚበልጥ ዦሮዬ ሰማች።
፮፤
በኃጢአተኞች ወገኖች መቅሠፍት ትመጣለች፥ በወንጀለኞችም ወገኖች ጥፋት ትመጣለች።
፯፤ በኃይላቸው
የታመኑ የቀደሙ አርበኞችም ሰውነታቸውን አላዳኑም።
፰፤ ሎጥ ለኖረባቸው ራሳቸውን ላኮሩ፥ ሎጥንም ላስጸየፉት አገሮች
አልራራላቸውም።
፱፤ በኃጢአታቸው ጠፉ እንጂ፥ ኃጢአተኞች ወገኖችንም ይቅር አላላቸውም።
፲፤ የተሰበሰቡ
ልቦናቸውንም ያከፉ፥ እነዚህ ስሳ እልፍ አርበኞች ናቸው።
፲፪፤
ቊጣውእንደ ቸርነቱ ብዛት መጠን ነው፥ ሰውንም እንደ ሥራው ይከፍለዋል።
፲፫፤ ኃጢአተኛ ሰው ከመከራ አያመልጥም፥ ደግ ሰውም የትዕግሥቱን ዋጋ
አያጣም።
፲፬፤ ምጽዋቱ
ሁሉ ይቅርታን ያመጣል፥ ሰውም እንደ ሥራው ዋጋውን ያገኛል።
፲፭፤ ኃጢአት
ሠርተህ ከእግዚአብሔር አመልጣለሁ በሰማያትም የሚያገኘኝ የለም።
፲፯፤
የሰውነቴስ ቊጥሯ ለዓለሙ ሁሉ ምንድ ነው አትበል።
፲፰፤ እነሆ፦ ይህ ሰማይ፥ ከሰማይም በላይ ያለ ሰማይ፣ ከሰማይም በታች
ያለ ውቅያኖስ፣ ምድርም በመዓት በጐበኛቸው ጊዜ ሁሉ ያልፋሉ።
፲፱፤
ተራሮችም፥ የምድርም መሠረት በመዓት ባያቸው ጊዜ ይንቀጠቀጣሉ፤ ይነዋወጣሉ።
፳፤ ይህንንም
ልብ አያስበውም፥ የእግዚአብሔርን ሥራውን ማን ያውቃል፣ ገናንነቱስ ጠንቅቆ ማን ያውቃል።
፳፩፤ ሰው የማያየው ፍጥረቱ ነፋስ ነው፤ ከሰው የተሠወረ፥ ፍጥረቱም ብዙ
ነው።
፳፪፤ እውነት
ሥራ መሥራትን ማን ያሥተምራል፥ የይቅርታውንስ አለኝታ ማን ደጅ ይጠናል።
፳፫፤ አእምሮ የሌለው ሰው እንዲህ ያስባል፥ ሰነፍ በደለኛ ሰውም ስንፍናን
ያስባል።
የእግዚያብሔር ጥበብ በሥነ ፍጥረት
፳፬፤ ልጄ፦ ስማኝ፥ ጥበብንም ተማር፣ ነገሬንም ከልቦናህ አድምጠው።
፳፭፤ በልቦናህ መርምረህ ጥበብን ግለጣት፥ የትምህርትህንም ምሥጢሯን
ተረዳ።
፳፮፤
የእግዚአብሔር ፍጥረቱ፥ ለይኩን ባለው ቃሉ ተፈጠረ፤ በየወገናቸውም ሥራቸውን አየ።
፳፯፤ ይህ
ዓለም፥ ጸንቶ በሚኖር ገንዘብ ሥራውን ሁሉ አዘጋጀ፣ ሠራዊታቸውንም በየወገናቸው አዘጋጀ፤ ይኸንን የፈጠራቸው እግዚአብሔር፥
አይራብም፣ አይጠማም። ብርሃናቸውም አይፈጸምም።
፳፰፤ አንዱ
ካንዱ ጋር አይጨናነቅም፥ ለዘለዓለሙ ከቃሉ አይወጡም።
፳፱፤ ከዚህ በኋላ፥ እግዚአብሔር ይህን ዓለም ጎበኘ፣ ዝናብንም አጠገበ።
፴፤ በደማዊት ነፍስ ሕያው የሆነ ፍጥረት ሁሉ በዚህ ዓለም መላ
መመለሻቸውም ወደ መቃብር ነው።